Die folgenden Informationen sind für Bethel Ethiopian and Eritrean Evangelical Church of Ann Arbor, Michigan verfügbar:
Bethel Evangelical Church of Michigan (Bethel-ECM) is an evangelical church for Ethiopians and Eritreans living in Michigan.
Bethel Ethiopian and Eritrean Evangelical Church of Ann Arbor, Michigan Finden Sie unter der folgenden Adresse:
Schauen sie auf der Karte nach, um zu sehen, wo sie Bethel Ethiopian and Eritrean Evangelical Church of Ann Arbor, Michigan finden können.
Die folgenden Kategorien beschreiben Bethel Ethiopian and Eritrean Evangelical Church of Ann Arbor, Michigan:
Use the following telephone number to get in touch with Bethel Ethiopian and Eritrean Evangelical Church of Ann Arbor, Michigan:
Auf der folgenden Website nach Bethel Ethiopian and Eritrean Evangelical Church of Ann Arbor, Michigan suchen:
Was ist in letzter Zeit bei Bethel Ethiopian and Eritrean Evangelical Church of Ann Arbor, Michigan passiert?? Hier finden Sie relevante Neuigkeiten:
https://www.youtube.com/watch?v=6mCA2HCouM8
እግዚአብሄር ለኢያሱ የተናገረዉ "አይዞህ በርታ" ባለብዙ ነጥቦች ከመሆኑ አንጻር ለኢያሱም ሆነ ለኛ በጣም እንደሚያስፈልገን ግልጽ ነዉ። ኢያሱ የሙሴን ሃላፊነት በሙሉ ተረክቦ የእግዚአብሄርን ህዝብ ወደ ተስፋቸዉ ምድር የሚያደርስ አዲስ መሪ ነበርና። እግዚአብሄር ለኢያሱ የምመክረዉ ቢዘረዘር፤ ሰላምን፤ እረፍትን፤ ብርታትን፤ቆራጥነትን፤ ተስፋ ቃልን፤ ስነምግባርን፤ ጸጋን፤ የቃሉን ሥልጣን፤ በመንፈሳዊ ህይወት ማደግን፤ በቃሉ ማሰላሰልን፤ እግዚአብሄርን ማክበር፤ ልበ ሙሉነትን፤ ቃሉን ከአባቶች በክብር መቀበልን፤ መታዘዝን፤ መልካም ሃሳብና፤ አስተምሮን፤ ያጠቃልላል። የኢያሱን መልዕክት ለመረዳት እነዚህን ነጥቦት ማብራራት የለብኝም። በድፍኑ ከዚህ "አይዞህ በርታ" የምንማረዉ መሪህ ሃሳብ ይህ ነዉ። የእግዚአብሄርን ቃል ተቀብሎ በሥራ ከመተርጎም የበለጠ፤ ሳይሸርፉ ስይጨምሩ በትክክል ከመረዳት ዉጪ መከናወን ፈጽሞ የለም። በዓለም እይታ መሳካትና መከናወን ከዚይ ይለያል። ከወደዳችሁ እናንተ ዘርዝሩ። የቃሉን አንኳር በድጋሚ ለማስተላለፍ ያህል፤ በረከት ከሃላፊነት ጋር ነዉና እግዚአብሄር ይከናወንልሃል ካለዉ ዉጪ የዓለምን ዝና ምን ብናግበሰብስ መከናወን አይደለም። በዚህ ዋና ምክር ጌታ እንድያስተምረን ጸሎታችን ነዉ። አሜን!
የሚሹት ደስ እንድላቸዉ መላእክት ተልኮላቸው እህቶች/እናቶች የመጀመሪያዉን የምስራች ሰምተዋል። በኢየሱስ ላመኑት ቀዳሚ መስካሪዎች መላእክት በመሆናቸው ደስ ይለናል። ከተጨባጭ ማስረጃ ጋር ሞትና ትንሣኤ ያለውን ኢየሱስ እናመልካለን። የሙታን ትንሳኤ ምክኒያት የሆነን የኢየሱስ ሞትና ትንሣኤ ነዉና ይህም ግሩም መገለጥ ነዉ። እግዚአብሔር ይመስገን። ሰዉ ሁሉ ወደዚህ መገለጥ ተጠርቷል። ይህንን ልብ ብላችሁ ለምታከብሩ እንኳን አደረሳችህ!!!
ለመሪዎች መጸለይ ዜጎች ለመሪዎቻቸዉ መጸለይ አስፈላጊ ነዉ። መልካምም ሆኑ አልሆኑ ለመሪዎች መጸለይ መጽሐፍ ቅዱስ ያዛል። የአገር መሪዎች፤ የቤተክርስቲያን መሪዎች••• ሁሉም መሪዎች ጸሎት ያፈልጋቸዋል። 1 ጢም 2፡ 1-2 "እንግዲህ እግዚአብሔርን በመምሰልና በጭምትነት ሁሉ ጸጥና ዝግ ብለን እንድንኖር፥ ልመናና ጸሎት ምልጃም ምስጋናም ስለ ሰዎች ሁሉ ስለ ነገሥታትና ስለ መኳንንትም ሁሉ እንዲደረጉ ከሁሉ በፊት እመክራለሁ። 3-4 ሰዎች ሁሉ ሊድኑና እውነቱን ወደ ማወቅ ሊደርሱ በሚወድ በእግዚአብሔር በመድኃኒታችን ፊት መልካምና ደስ የሚያሰኝ ይህ ነው።" ከሁሉ በላይ ለሰዎች ሁሉ ነገሥታትና መኳንንትን ጨምሮ የምንጸልይበት ምክኒያት ይድኑ ዘንድ ነዉ። ይህ ደግም እግዚአብሄርን ያስደስታል። የሰዉ ሁሉ በክርስቶስ መዳን የአምላካችን የዘለዓለም ሃስቡ ነዉ። ሰዉን ለማዳን እርሱ የማያደርገዉ ምንም ነገር የለም። አንድ ልጁን እስከመስጠት ድረስ ሰዉን ይወዳል “ዮሐ 3፡16 በእርሱ የሚያምን ሁሉ የዘላለም ሕይወት እንዲኖረው እንጂ እንዳይጠፋ እግዚአብሔር አንድያ ልጁን እስኪሰጥ ድረስ ዓለሙን እንዲሁ ወዶአልና” ነብዩ ሲናገር፤ ኢሥራኤሎችም ለስደት በሄዱበት ለባቢሎን እንዲጸልዩ ያሳስባቸዋል እንዲህ ሲል “7 በእርስዋ ሰላም ይሆንላችኋልና ወደ እርስዋ ላስማርክኋችሁ ከተማ ሰላምን ፈልጉ፥ ስለ እርስዋም ወደ እግዚአብሔር ጸልዩ።” ኤር 29፡7። ሐዋሪያዉ ጳዉሎስ ሲናገር “ •••ከእግዚአብሔር ካልተገኘ በቀር ሥልጣን የለምና፤ ያሉትም ባለ ሥልጣኖች በእግዚአብሔር የተሾሙ ናቸው።” ሮሜ 13፡1። ሆኖም አብዛኛዉቹ የምድር ነገሥታት የሾማቸዉን እግዚአብሄርን አያዉቁም። አይፈሩትም። ስለዚህም መጨረሻቸዉ ምልካም አይደለም። ሹመት እግዚአብሄርን ማገለገል መሆን ሲገባዉ አንዳንዶች ከመታበያቸዉ የተነሳ በምድር እያሉ ታላቅ ዉድቀት ብሎም የዘለኣለም ታላቅ ፍርድ ያገኛቸዋል። ይህንን ስናዉቅ ታዲያ እንጸልይላቸዉ ዘንድ ምን ያህል አስፈላጊ ነዉ። ለአለቆቻችን መጸለይ ጊደታችንም ጥቅማችንም ነዉ። ነብዩ ኤርሚያስ እንደጻፈልን ዋናዉ ጥቅማችን ሰላም ነዉ። ስንጽልይላቸዉ ሰላም ይሆናል። ጎራዴአቸዉ ከሰገባ አይወጣብንም። የወጣዉም ይመለሳል። ጎራዴ ስል መትረየስን ይጨምራል። ሰዉን የሚገድሉበት ሁሉ ማለቴ ነዉ። ጸሎት ከጎራዴ የበለጠ ሃይል አለዉ። ሰላም የሚያስጠብቅበትን ወደ ህዝቡ ያዞረ እንደሆነ፤ ቤተሰባችን፥ መሥሪያ ቤታችን፥ ትምህርት ቤታችን፥ መዉጣት መግባታችን ጎራዴ በታጠቁት ሰላም ያጣል። ከተማዎቻችንና መንደሮቻችን ይታውካሉ። መንስኤዉ ያም ሆነ ይህ በአገራችን ኢትዮጵያ የደረሰው ሰላም ማጣት እግዚአብሄር ስላልተፈራ መሆኑ ግልጽ ነዉ። በኢትዮጵያ አገራችን አሁን አዲስ መሪ ዶ/ር አቢይ የሚባሉ ተመርጠዋልና እግዚአብሄር እንዲረዳቸዉ እንጸልይላቸዉ። ለአንድ መሪ ከጸሎት የበለጠ እርዳታ አለ ብዬ አለምንም። መንግሥታትን የሚሾመዉ እግዚአብሄር እስከሆነ ድረስ የእግዚአብሄር አገልጋዮች መሆናቸዉ ግልጽ ነዉ። ስንቶቹ ይህንን ያዉቃሉ? እንጸልይላቸዉ ዘንድ እጅጉን ያስፈላጋል። ዊሊያም ቲንዴል የሚባል የቤተክርስቲያን አባት የእንግሊዝ ንጉሥ አቃጥሎ እየገደለው የተናገረዉ የመጨረሽ ቃል ስለጸሎት አስፈላጊነት አሳምሮ ያስረዳናል፡ “ጌታ ሆይ የእንግሊዝን ንጉሥ ዓይን ክፈት” አለ። የትኛዉም ንጉስ ዓይኑ እያየ መልካምን ዜጋ አይገድልም። ስለዚህ ለገዢውቻችን ልንጸልይላቸዉ ይገባል። በጭምትነት ሁሉ ጸጥና ዝግ ብለን እንድንኖር ለባለሥልጣኖች እንድንጽልይ ተጠርተናል። መልካም ባለሥልጣኖች ጸሎታችን እንድሚያስፈልጋቸዉ ሁሉ ከፉን የሚያደርጉ ባለሥላጥኖችም ጸሎታችን ያስፈልጋቸዋል። አገር ማስተዳደር ቀላል እንድማይሆን መገመት አያዳግተንም። አገር መሪነት ከክፉ አድራጊዎች ይልቅ ለመልካም አድራጊዎች የበለጠ ይከብዳል። ምክኒያቱም እነዚያዎቹ ምናልባት ለራሳቸዉ ብቻ ሲያስቡ እነኚሆቹ ግን ለብዙዎች ሃላፊነትን የሚሸከሙ፤ ለትዉልድ ሁሉ የሚያስቡ፤ ለአገር የሚጨነቁ ስለሆነ። በመልካም የሚያስተዳድር/የሚመራ እግዚአብሄርንና ህዝብን የሚያገለግሉ እንደመሆናቸዉ ከልክ በላይ የሆነ ሃላፊነትን የሚሸከሙ ናቸዉ። መልካም ባለሥልጣኖች ወደ ተቸገሩትና ወደተጎዱት የሚሄዱ ናቸዉና ጊዜና ጉልበት አይበቃቸዉም። ስለዚህ ልንጽልይላቸዉ ይገባል። መልካም የሚያስተዳድሩ ሰዎች ምስጋናና ሀዘኔታ እርዳታና ጸሎት ያስፈልጋቸዋል። ልንታገሳቸዉና ልናግዛቸውም ይገባል። ሸክማቸዉ ከባድና ዉስብስብ ነዉ። ባጠቃላይ መልካም መሪዎች ባተሌ አገጋዮች ሲሆኑ ክፉ ገዢዎች ግን ነጣቂዎችና በሊታዎች ሊሆኑ ይችላሉ። በመጨረሻ ለመሪዎቻችን ምን እንጸልይላቸዉ? • መዳን እንዲሆንላቸዉ • እኛን በብቃት እንድመሩን እግዚአብሔር ደግሞ እንዲመራቸዉ • እግዚአብሄር ጥበብን እንዲሰጣቸዉ • ክፉና ደጉን ለይተዉ እንዲያዉቁ • መልካም መካሪዎችና አማካሪዎችን እግዚአብሄር እንዲሰጣቸዉ • እግዚአብሄር ለመንግሥቱና ለህዝቡ ብሎም ለክብሩ እንዲጠቀምባቸዉ • ሃይልና ብርታ እንዲሰጣቸዉ • እንዳይደክሙና እንዳይዝሉ • ለቤተሰቦቻቸዉ ጠንነትና ሰላም በመጨረሻ፡ መላዉ የኢትዮጵያ ወገኖች መሪዎቻችን ለሚያስፈልጋቸዉ ሁሉ በእግዚአብሄር ፊት ዘወትር እናቀርባቸዉ ዘንድ እጠይቃለሁ።
ያለኝ ይበቃኛል January 20, 2018 ይህንን አረፍተ ነገር ስታነቡ “እርግጠኛ ነህ?” ትሉ ይሆናል። ክርስትያኖች ይህንን ቃል አፍ ሞልተዉ መናገር የሚችሉብት በቂ ምክኒያቶች አሉ። ነገር ግን ብዙዎቻችን በእግዚአንሄር ቤት ስንኖር ልንተገብር ቀርቶ ትክክል የሆነ ትዕዝዝ እንደሆነ የማንረዳ ብዙዎች ነን። ከሁሉ አስቀድሞ የቃሉ ትርጉም እንደሚከተለዉ ተገልጿል። በአእምሮም ሆነ በስሜት ባለንበት ሁኔታ ሁሉ መርካት ወይም መረጋጋት ማለት ነዉ (መዝገበ ቃላት)። መጽሐፍ ቅዱስ በብዙ የሚያስተምረን ትዕዛዝም ምክርም ነዉ። በመጽሐፍ ቅዱስ ካስተማሩት መካከል ጌታችን ኢየሱስ ዋነኛዉ እንደሆነ እናዉቃለን። ጌታ ኢየሱስ በማቴዎስ ዌንጌል “25 ስለዚህ እላችኋለሁ፥ ስለ ነፍሳችሁ በምትበሉትና በምትጠጡት፥ ወይም ስለ ሰውነታችሁ በምትለብሱት አትጨነቁ፤ ነፍስ ከመብል ሰውነትም ከልብስ አይበልጥምን?” ማተ 6፡25። ባለን ረክቶ ከመኖር የሚገድቡ ነገሮችን ከዘረዘረ በሗላ ደግሞ ማተ 6 ላይ “33 ነገር ግን አስቀድማችሁ የእግዚአብሔርን መንግሥት ጽድቁንም ፈልጉ፥ ይህም ሁሉ ይጨመርላችኋል። 34 ነገ ለራሱ ይጨነቃልና ለነገ አትጨነቁ፤ ለቀኑ ክፋቱ ይበቃዋል።” አለ። ነገር ግን ስንቶቻችን ይህንን ቃል የራሳችን አድርገን እንኖርበት ይሆን። ከዚህ ችግር አንጻር ለአንዳንዶቻችን ይጠቅም እንደሆነ በሚል ምክሩን ደግሜ ላሳስበን ወደድኩ። አስቀድሞ እንደጌታ ኢየሱስ ትምህርት ይህ ቃል ቀጥተኛ ትዕዛዝ መሆኑ እንዲገባን ያስፈልጋል። ትዕዛዙን መጠበቅ ደግሞ የደቀመዛሙርት ሃላፊነትና ለጌታ ያለን የፍቅሩ መሠረት እንደሆነ ሁሉ ቆም ብለን ማሰላሰል ያለብን ጉዳይ ነዉ። ጌታ ይህንን ስናገር ለምንወደዉ ሁሉ አለማስተውላችን ከፍተኛ ችግር በመሆኑ አንጻር መፍትሄዉ ደግሞ ምንኛ ጠቃሚ እንደሆነ ስለሚያዉቅ ነዉ። በራስ ኑሮ አለመርካት በዘመኑ የብዙ የጤንነት መታወክ ምክኒያት እንደሆነና ወደዚህ መረዳት ስንመጣ ግን ምንኟ ፈዉስ እንድሚሆን ማወቅ አለብን። “ያለኝ ይበቃኛል” ከመጥፋቱ የተነሳ አማኞች አላማኞችን መስለን እንዳለ ጥርጥር የለዉም። ምክኒያቱም ማተዎስ ላይ ጌታ ሲናገር “32 ይህንስ ሁሉ አሕዛብ ይፈልጋሉ፤ ይህ ሁሉ እንዲያስፈልጋችሁ የሰማዩ አባታችሁ ያውቃልና።” በማለት አስረግጦ ያስተምረናል። ይህ የሃጢአት ሥር ሁላችንንም በአንድ የአላማኝነት ጎራ ያስቀምጠናል፤ ማለት ነዉ። ከጌታችን ሌላ ደግሞ “ያለኝ ይበቃኛል”ን ያስተማረዉ ይዚህን መንፈሳዉ ሚስጥር በህይወቱ ያዉቅ የነበረዉ ቅዱስ ጳዉሎስ ነዉ። ሓዋሪያዉ ጳዉሎስ በብዙ ስለጽድቅና ስለእምነት የተንገለታ ሰዉ ነዉ። አርባ ግርፋት አምስት ጊዜ የተገረፈ፤ 25 ሦስት ጊዜ በበትር የተመታ፤ አንድ ጊዜ በድንጋይ የተወገረ፤ መርከቡ ሦስት ጊዜ ይተሰበረበት፤ ሌሊትና ቀን በባሕር ውስጥ የኖረ፤ ብዙ ጊዜ በመንገድ የሄደ፤ በወንዝ ፍርሃት፥ በወንበዴዎች ፍርሃት፥ በወገኑ ፍርሃት ሳይቀር፥ በአሕዛብ ፍርሃት፥ በከተማ ፍርሃት፥ በምድረ በዳ ፍርሃት፥ በባሕር ፍርሃት፥ በውሸተኞች ወንድሞች ፍርሃት የነበረበት፤ ብዙ የደከመ፤ ብዙ የጣረ፤ ብዙ እንቅልፍ ያጣ፥ ራብና ጥም የጎዳዉ፥ ብርድና ራቁትነት ያስችገረዉ። እንደነበረ ይነግረናል። 2ቆሮ 11፡23••• ያ ሁሉ ሲሆን ቅዱስ ጳዉሎስ ያለዉ እንዲህ ነበር “11 ይህን ስል ስለ ጉድለት አልልም፤ የምኖርበት ኑሮ ይበቃኛል ማለትን ተምሬአለሁና።12 መዋረድንም አውቃለሁ መብዛትንም አውቃለሁ፤ በእያንዳንዱ ነገር በነገርም ሁሉ መጥገብንና መራብንም መብዛትንና መጉደልን ተምሬአለሁ።13 ኃይልን በሚሰጠኝ በክርስቶስ ሁሉን እችላለሁ።’ ፊሊ 4። “የምኖርበት ኑሮ ይበቃኛል” የተጻፈልን ለትምህርታችን ነዉ። የዕብራዉ ጸሐፊም ሲያስተምረን ይህን ችግር አስመልክቶ እንዲ ብሏል። “5አካሄዳችሁ ገንዘብን ያለ መውደድ ይሁን፥ ያላችሁም ይብቃችሁ፤ እርሱ ራሱ። አልለቅህም ከቶም አልተውህም ብሎአልና፤6ስለዚህ በድፍረት። ጌታ ይረዳኛልና አልፈራም፤ ሰው ምን ያደርገኛል? እንላለን።” ዕብ 13 ነገር ግን የዓለም ህዝብ በብዙ አለመርካት ይኖራል ደግሞም ሳይረካ የሚሞቱ ጥቂቶች አይደሉም። መቼም በጠረጴዛዉ እንጀራ ያለዉ፥ በአናቱ ላይ ጣሪያ ያለዉ፥ በሰዉነቱ ላይ ልብስ ያለዉ በአሁን የህዝብ ቀመር ከብዙቹ የተሻለ እንደሆነ ይታወቃል። በእግሩም ላይ ጫማ ያለዉ እንደዚሁ። በአገራችን ኢትዮጵያ ደግሞ ከሁሉ የከፋ የሰዉ ልጅ ኑሮ እየተመዘገበ ይገኛል። ነገር ግን በነፍሰወከፍ የቤተሰቦች የብድር ዕዳ በአሜሪካ $16,000 በላይ እንደሆነ ይነገራል። በነገራችን ላይ ገንዘብ እርካታን እንድማያመጣ የሰነበተ እዉነት ነዉ። በታሪክ ባለጸጋ የሆነዉ ንጉሥ ሰሎሞ እንዲህ ብሏል። “10፤ ብርን የሚወድድ ሰው ብርን አይጠግብም፤ ባለጠግነትንም የሚወድድ ትርፉን አይጠግብም፤ ይህም ደግሞ ከንቱ ነው።” መክ 5:10. ስለዚህ “ያለኝ ይበቃኛል” የሚገነዉ ከብር እንዳልሆነ ተምረናል። ሦስት ነገሮችን በማድረግ ያ እርካታ እንድሚመጣ መምከር እፈልጋለሁ። 1) እግዚአብሄርን ማስቀደምና በተስፈ ቃሉ መታመን 2) የቻልነዉን ያህል በመሥራት፤ ትርፉን በመስጠትና በዋናዉ መኖር 3) በሆነዉም ባልሆነዉም ደግሞ አለመጨነቅ “ኑሮዬ ይበቃኛል’ን አስመልክቶ ሦስቱም የእግዚአብሄር ጸጋ ዉጤቶች በመሆናቸዉ ባለሦስት እግር መቀመጫዎች ናቸዉ። በነዚህ አርፎ የተቀመጠ አይወድቅም። የሶስቱን መሠረቶች ጉዳይ በቀጣይ እንመለስባቸዋለን። በአንድ የመጨረሻ ጥቅስ ልሰናበታችሁ። “6 እንግዲህ በጊዜው ከፍ እንዲያደርጋችሁ ከኃይለኛው ከእግዚአብሔር እጅ በታች ራሳችሁን አዋርዱ፤7 እርሱ ስለ እናንተ ያስባልና የሚያስጨንቃችሁን ሁሉ በእርሱ ላይ ጣሉት።” 1ጰጥ 5 ዓለሙ ፊጤ
የፍቅር ጥሪ ዓ.ም. 2018 መቁጠር ጀምሯል። ዘመን ሁሉ ወደ ፍጻሜዉ ይቸኩላል። መጽሐፍ ቅዱስ እንደሚያስተምረን ድምዳሜዉ መልካም እንደሆነ ይታወቃል። ታዲያ በክርስቶስ ለሆኑት። በከርስቶስ ላልሆኑት ደግሞ እድሉ ገና አለ። የመዳን ቀን ግን ዛሬ ነዉ ይላልና (2ቆሮ 6፡2) ነጌ አስተማማኝ ቀን አይደለችም። አስተማማኝ እግዚአብሔር ብቻ ነዉ። በቃሉ መሠረት ዛሬዉኑ ወደ ጌታ እንመለስ። የእግዚአብሄር ቃል በሮሜ መጽሐፍ እንደሚለዉ " እንግዲህ በክርስቶስ ኢየሱስ ላሉት አሁን ኵነኔ የለባቸውም።" ሮሜ 8፡1 ዓለሙ ፊጤ
መልካም አዲስ ዓመት !!!!!!! ከሁሉ በፊት ለአምላካችን እግዚአብሄር ምስጋና ይሁን። አቅራቦቱን ሳያቋርጥ ዓመታትን አሻግሮ 2018 ዓም ላደረሰን ጌታ እግዚአብሔር ዉዳሴ ይገባዋልና። በተለይም በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ልጆቹ አድርጎ ለመረጠን ምስጋና ለእግዚአብሄር እናቀርባለን። ይህም ታላቅነቱን፤ መሃሪነቱን፤ ፍቅሩንና ባለጸጋነቱን ያሳያል። ስለዚህ ማንነቱና ክብሩ የአምልኮአችን ዋና ምክኒያት ነዉ። በተጨማሪም እግዚአብሄርን የምናመሰግንበት ብዙ ምክኒያቶች አሉ። ወደሇላ ስንመለከት ለሚያስፈልገን ነገር ሁሉ እግዚአብሄር በ2017 እና ከዚያም በፊት እንዴት በምድራዊ ነገር እንደባረከን እናስባለን። ክፉዎች ለማጥፋት ሃይልን በተሞሉበት በዚህ ዘመን ብዙዎች ከተጠቁበት ሃጢአት፤ ጉስቁልና፤ እንግልትና ሞት ጠብቆ እግዚአብሄር ተጨማሪ ዘመነ ምህረት ስለሰጠን ለእግዚአብሄር ምስጋና እናቀርባለን። ስለራሳችንና ስለብዙዎች በዚህ ሁኔታ ስናመሰግን፤ የዲያብሎስ፤ ሰራዊቱ የሆኑት መናፍስትና ሰዎች ሰለባ ለሆኑት ደግሞ ምህረትንና ይቅርታን እንጠይቃለን። የጥፋትና የክፋት መልዕክተኛ ለሆኑት ሰዎች ደግሞ ምህረትንና መመለስን በተሰበረ ልብ ከመሃሪዉ ጌታችን እንለምናለን። ወደፊትም ስንመለከት ደግሞ ከመረዳት በላይ የሆኑ በረከቶቹ ይጠብቁናል። “1ቆሮ 2፣9…ዓይን ያላየችው ጆሮም ያልሰማው በሰውም ልብ ያልታሰበው እግዚአብሔር ለሚወዱት ያዘጋጀው ተብሎ እንድተጻፈ፥ እንዲህ እንናገራለን።” በመጪዉ ዓመታት እግዚአብሄር በሰጠን ቀናት የምንፈጽማቸዉ ብርቱ ነገሮች ስላሉ ልባችን በጎ ነገሮችን ሰርቶ ለማለፍ ወደዚያ ልቸኩል ይገባል። ማንም ክርስቲያን በመጨረሻ "…ታማኝ ባሪያ…” ማቴ 25፣23 የሚታሰኘዉን ሽልማትና ርስት ለማግኘት ይፈጥናል። ለዚያም ሌላ አዲስ ዓመት ስለሰጠን ጌታችን እጅጉን የተባረክ ይሁን። ስለዚህ በዚህ ምድር ለመኖራችን ምክኒያት የሆነዉን የእግዚአብሄርን ሥራ ሁሉ ቸል እንዳንል ለወገኖች ሁሉ ጸሎታችንና ምኞታችን ነዉ። በመንፈስ ቅዱስ እርዳታ የበለጠ እንድንኖርለት 2018 ልዩ የበረከት፣ የሰላም፣ የጤንነት፣ የፍሬያማነት፣ እና የእድገት ዓመት እንዲሆንልን ጸሎታችንና ምኞታችን ነዉ። ለዓመቱ መሪህ ቃል፡ መዝሙር 18፡48 “ከጠላቶቼ የሚታደገኝ እርሱ ነው፤ በእኔም ላይ ከቆሙ ከፍ ከፍ ታደርገኛለህ፥ ከግፈኛ ሰው ታድነኛለህ። 49 አቤቱ፥ ስለዚህ በአሕዛብ ዘንድ አመሰግንሃለሁ፥ ለስምህም እዘምራለሁ።” ለማሰላሰል፡ መዝሙር 143 የደስታ፤ የሰላም፤ የመዳንና የድል ዓመት ይሁንላችሁ!!! ዓለሙ ፊጤ (ከቤቴል ቤተ ክርስቲያን)
Dear Friends, Christmas celebration is here and we would like to say Mary Christmas to every Brethren who loved us, endured with us and ministered to us during the year 2017. We extend our Mary Christmas to those whom we had the honor of ministering to during the year. Mary Christmas to all Christ died for, gave His life for, those who come to Him, love Him and believe in Him. With Christmas every year we are reminded of gifts. Real Christmas is a special love gift. This is the gift of God His only begotten Son, Jesus Christ. Through the gift of God in Jesus Christ we would experience the grace and peace of our God. The gift of God is eternal life, the heavenly Kingdom, true life after we die. The Lord Jesus Christ, our Christmas, is the reason for the season, and for the history of the universe, for the created order, for everything. Above all just remember what our loving God has done for us during the year and in eternity. Those of you who love Christmas go and read the Bible, where you meet the Lord, Jesus Christ - the subject of the entire story, where you will be filled with knowing your savior, where you start to admire how God did it through incarnation. There is no end to the wisdom there; it contains light to your path, food for your life, and comfort to your soul. When you find it, it should fill your memory, direct the desire of your heart, and guide the walk along your journey, it becomes your treasured assurance; it reveals the hope of all glory. If you do not know Christ, He is knocking on your door, preparing your heart, taking you to places. If you still do not believe, He will tell you He died for you, He will show you the wounds of His hands and His side. Who ever the Father draws near to Him He eventually gain your will, then follows your repentance, praise and worship for the joy you did it. Our prayer this coming new year is for those of you, who would come to the Lord and experience the real life only Jesus can offer. Afterwards, no regret in your thinking, no return to your old life, just to follow the word of God like the traveler's map, the pilgrim's staff, and the pilot's compass. Once in your hands, the Scripture will protect you as the soldier's sword, change you from inside out; encourage you to finish the journey. Yet, remember, it involves the highest responsibility; diligence is reward in it, tampering with its sacred contents is condemnation (Rev 22:19). If we can be of any help please contact us so that we will pray for you, pray with you, we will join together for the common pilgrimage and celebrate the king of glory who was born for our redemption and salvation. Otherwise we would be under the wrath of God, sting of death and power of the wicked and wickedness. Mary Christmas !!!!!!! Alemu Fite
worship with singer Kaleab Tsegaye at the 2017 annual Bethel conference
Evangelist Yared Tilahun Preaching "yeEgziabher Mengist" part 1 - Bethel annual conference 2017
Evangelist Yared Tilahun preaching "yeEgziabher Mengist" part 2 at the 2017 annual Bethel conference
Hier finden Sie Bilder von Bethel Ethiopian and Eritrean Evangelical Church of Ann Arbor, Michigan:
Hier finden Sie Videos von Bethel Ethiopian and Eritrean Evangelical Church of Ann Arbor, Michigan:
worship with singer Kaleab Tsegaye at the 2017 annual Bethel conference
Worship with Singer Kaleab Tsegaye at the Bethel annual 2017 conference
Auch diese Restaurants in der Nähe ansehen:
Auch diese Hotels in der Nähe ansehen:
Auch diese Immobilienmakler in der Nähe ansehen:
Auch diese Hair salons in der Nähe ansehen: